Tag Archives: Afar and Somali conflict

ከአፋር ህዝብ ፓርቲ (አህፓ) ወቅታዊውን የአፋርና ሶማሊ ግጭትን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ

Posted on by 0 comment

ታህሣሥ 19/2013

በሀገራችን ኢትዮጵያ ካለፉት ሁለት ዓመት ተኩል በፊት በፌደራሊዝም ስም በሀገራችን ተንሰራፍቶ የነበረው ፍፁም አምባ ገነናዊ ስርዓት ተወግዶ ተስፋ ሰጭ ለውጥ በመምጣቱ የሀገራችን ህዝቦች ከነበረው አፋኝ ስርኣት እፎይታን አግንተዋል፡፡
ለውጡ ህዝባችን በፈለገው መጠንና በተፈለገው አቅጣጫ ሙሉ በሙሉ ባይሄድም በኢኮኖሚ በፖለቲካና በማህበራዊ ዘርፎች አበረታች የሆኑ ለውጦች ታይተዋል፡፡ ይሁን እንጂ ለውጡ የመጣባቸውና የሀገራችንን እድገት እና ልማት የማይመኙ በቅርብም በሩቅም ያሉ ሀይሎች የለውጡን ሂደት ለማደናቀፍ ከለውጡ ማግስት ጀመሮ በሀገራችን ኢትዮጵያ ሰላምና መረጋጋት አንዲሁም አብሮነትና አንድነት እዳይኖር እንቅልፍ አጥተው ሌት ተቀን በመስራት ሀገራችን ተረጋግታ ለውጡ ግቡን እንዳይመታ እዛም እዚህም ግጭት በመፍጠር ለውጡን ለማደናቀፍ እነዚህ የጁንታው ርዝራዦች ብዙ እየታተሩ ይገኛሉ፡፡

ተጨማሪ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

Stop systmatic eviction of Afar pastoralists by Somali Region Special Militia

Posted on by 0 comment

ከአፋር ህዝብ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ

የአፋር ህዝብ ፓርቲ (አህፓ) ሀገራዊውን የፖለቲካ ምህዳር መስፋትን ተከትሎ ወደ ሀገር ከተመለሰ እነሆ ሁለት ዓመት አስቆጥሯል። ፓርቲያችን ወደ ሃገር ከገባበት ጊዜ ጀምሮ በተለያዩ ፖለቲካዊና ማህበራዊ መስኮች ሃገራዊ ግዴታውን እየተወጣ ይገኛል። የአፋር ህዝብ ፓርቲ በሃገራችን የተጀመረውን ረፎርም በአጭር ጊዜ ዉስጥ ያስመዘገባቸው የለውጥ ሂደቶችን ይደግፋል ያበረታታልም። ይሁንና በዚህ የለውጥ ሂደት ዉስጥ ወክለነዋል የምንለው የአፋር ህዝብ እንደ ህዝብ በሰላም የመኖር ዋስትና ፤ እንዲሁም እንደ ክልል ለመቀጠል የተደቀነበት ስጋት መቀረፍ አለመቻሉ እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል። ለዚህ ስጋት ምንጭ የሆነው በአፋር አርብቶ አደሮችና በሶማሌ ክልል መካከል ለዘመናት መፍትሄ ያላገኘው ጦርነት በዋናናት ሊጠቀስ ይችላል። ይህ ለዘመናት ሲንከባለል የመጣውና በሶማሌ ክልላዊ መንግስት አዝማችነት እየተካሄደ ያለዉን የግዛት ማስፋፋት ጦርነት ከፌዴራል መንግስት እልባት አለማግኘቱ መላውን የአፋር ህዝብ ቁጭትና ቁጣ ዉስጥ አስገብቶታል።

ፓርቲያችን ይህን ጉዳይ አስመልክቶ የፌደራል መንግስት ህገ-መንግስቱን ማዕከል ያደርገ መፍትሄ መሰጠት አለበት በማለት ላለፉት ሃያ ዓመታት ለኢትዮጵያ መንግስትና ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ሲያስታዉቅ ቆይቷል። ይሁንና የፌዴራል መንግስት እልባት ሳያገኝለት ወይም ፍላጎት ሳይኖረው በመቅረቱ የንጹሃን ዜጎቻችን ህይወት በየቀኑ እየተቀጠፈ ይገኛናል። ፓርቲያችንም ለህግ የበልይነትና ለዘላቂ ሰላም ቅድሚያ በመስጠት በሶማሌ ልዩ ሃይልና ከባድ መሳሪያ በታጠቁ የተቀናጁ ሐይሎች ህዝባችን እንደቅጠል ሲረግፍና ሲታመስ እያየን መንግስት መፍትሄ ያመጣል በሚል ተስፋ እስካሁ ታግሰናል።

ተጨማሪ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ