Tag Archives: አህፓ

ከአፋር ህዝብ ፓርቲ (አህፓ) ወቅታዊውን የአፋርና ሶማሊ ግጭትን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ

Posted on by 0 comment

ታህሣሥ 19/2013

በሀገራችን ኢትዮጵያ ካለፉት ሁለት ዓመት ተኩል በፊት በፌደራሊዝም ስም በሀገራችን ተንሰራፍቶ የነበረው ፍፁም አምባ ገነናዊ ስርዓት ተወግዶ ተስፋ ሰጭ ለውጥ በመምጣቱ የሀገራችን ህዝቦች ከነበረው አፋኝ ስርኣት እፎይታን አግንተዋል፡፡
ለውጡ ህዝባችን በፈለገው መጠንና በተፈለገው አቅጣጫ ሙሉ በሙሉ ባይሄድም በኢኮኖሚ በፖለቲካና በማህበራዊ ዘርፎች አበረታች የሆኑ ለውጦች ታይተዋል፡፡ ይሁን እንጂ ለውጡ የመጣባቸውና የሀገራችንን እድገት እና ልማት የማይመኙ በቅርብም በሩቅም ያሉ ሀይሎች የለውጡን ሂደት ለማደናቀፍ ከለውጡ ማግስት ጀመሮ በሀገራችን ኢትዮጵያ ሰላምና መረጋጋት አንዲሁም አብሮነትና አንድነት እዳይኖር እንቅልፍ አጥተው ሌት ተቀን በመስራት ሀገራችን ተረጋግታ ለውጡ ግቡን እንዳይመታ እዛም እዚህም ግጭት በመፍጠር ለውጡን ለማደናቀፍ እነዚህ የጁንታው ርዝራዦች ብዙ እየታተሩ ይገኛሉ፡፡

ተጨማሪ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ